ስፓርት
የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን የዓመቱ ምርጥ ቡድን ሽልማትን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን የዓለም አቀፉ የስፖርት ፕሬስ ማህበር (ኤአይፒኤስ) የ2024 የዓመቱ ምርጥ ቡድን ሽልማትን አሸነፈ፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ በ111 ሀገራት ከሚገኙ 518 ጋዜጠኞች በተሰበሰብ ድምፅ በአጠቃላይ 579 ነጥቦችን በማግኘት ሽልማቱን አሸንፏል።
የዩሮ 2024 አሸናፊው የስፔን ብሔራዊ ቡድን 552 ድምፆችን በማግኘት ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ የ2024 የሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው ሪያል ማድሪድ ደግሞ 532 ነጥቦችን በመያዝ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
ሊዮኔል ሜሲ፣ ላውታሮ…
Read More...
ብሬንትፎርድ ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ19ኛ ሣምት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ መርሐ-ግብር ብሬንትፎርድ ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ምሽት 2 ሠዓት ከ30 ላይ በጌቴክ ኮሙኒቲ ስታዲዬም በሚደረገው ጨዋታ አርሰናል በሊጉ ጠንካራ ከሆነው ብሬንትፎርድ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡
ጉዳት ላይ የነበረው የብሬንትፎርድ ግብ ጠባቂ ማርክ ፍሌከን…
አትሌት በሪሁ አረጋዊ የ10 ኪሎ ሜትር ክብረ ወሰንን ሰበረ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በስፔን ማድሪድ በተካሄደ ሳን ሲልቬስተር 2024 የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት በሪሁ አረጋዊ አዲስ ክበረወሰን በመስበር አሸንፏል፡፡
አትሌት በሪሁ ርቀቱን 26 ደቂቃ ከ32 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ክብረ ወሰን በማሻሻል ያሸነፈው፡፡
ኡጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ በአንድ ሰከንድ ዘግይቶ በመግባት…
የኢትዮጵያ ክለቦች አትሌቲክስ ሻምፒዮና መካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ክለቦች የአጭር፣ መካከለኛ፣ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል የርምጃ እና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡
ዛሬ በተካሄደው የሴቶች የርዝመት ዝላይ የፍፃሜ ውድድርም÷ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አትሌት ፓች ኡመድ 5 ነጥብ 95 ሜትር በመዝለል አንደኛ ሆናለች፡፡
በተመሳሳይ…
ዋይኒ ሩኒ ከፕሌይ ማውዝ ጋር ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ዋይኒ ሩኒ ከእንግሊዝ ሻምፒየን ሽፑ ቡድን ፕሌይ ማውዝ ጋር በስምምነት መለያየቱ ተሰምቷል፡፡
የ39 ዓመቱ የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞ ኮከብ እና የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አምበል ሩኒ÷ በተደረጉ 23 የቻምፒየን ሽፕ ጨዋታዎች 4 ጊዜ ሲያሸንፍ በ13ቱ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
በአሰልጣኝነት ዘመኑ ስኬት የራቀው…
ኢትዮጵያ በፎርፌ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)በሴቶች ከ17 ዓመት በታች ማጣሪያ ኢትዮጵያ በፎርፌ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፋለች፡፡
በሴቶች ከ17 ዓመት በታች ማጣሪያ አንደኛ ዙር ኢትዮጵያ እና ዚምባብዌ ጨዋታቸውን ለማድረግ መርሐ ግብር እንደወጣላቸው ይታወሳል።
ሆኖም ዚምባብዌ ከውድድሩ ራሷን ማግለሏን በማሳወቋ የደርሶ መልስ ጨዋታዎቹ…
ኤ ሲ ሚላን ፓውሎ ፎኔስካን ከኃላፊነት አነሳ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጣሊያን ሴሪ ኤው ክለብ ኤ ሲ ሚላን አሰልጣኝ ፓውሎ ፎኔስካን ከኃላፊነት ማሰናበቱን ይፋ አድርጓል፡፡
ክለቡ አሰልጣኙን ያሰናበተው ኤ ሲ ሚላን በትናንትናው ዕለት ከሮማ ጋር አንድ አቻ ከተለያየ በኋላ ነው፡፡
በሴሪ ኤው እንዲሁም በአውሮፓ መድረክ ቡድኑ እያስመዘገበ ያለው ደካማ እንቅስቃሴ ለስንብቱ ምክንያት መሆኑም…