Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አትሌት ሳሙኤል በአንድ ማይል የ2020ን ሁለተኛ ፈጣን ሰዓት አስመዘገበ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊው አትሌት ሳሙኤል ተፈራ በተያዘው የፈረንጆቹ ዓመት በአንድ ማይል ርቀር ሩጫ ሁለተኛውን የዓለም ፈጣን ሰዓት አስመዘገበ። በትናንትናው ዕለት በአየርላንድ አትሎን የአንድ ማይል የቤት ውስጥ ውድድር ተካሂዷል። አትሌት ሳሙኤል ተፈራ ርቀቱን በ3 ደቂቃ ከ55 ሰከንድ ከ86 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ ውድድሩን አሸንፏል። በዚህም በፈረንጆቹ 2020 በአንድ ማይል የቤት ውስጥ ውድድር ሁለተኛውን ፈጣን ሰዓት ማስመዝገብ ችሏል። ስኮትላንዳዊው ስኮት ኦሃር ርቀቱን በ3…
Read More...

በፕሪሚየር ሊጉ ወላይታ ድቻ ሃድያ ሆሳዕናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት የቀኑ ብቸኛ ጨዋታ በሃዋሳ ከተማ ስታዲየም ዛሬ ተካሂዷል። በዚህም ወላይታ ድቻ ሃድያ ሆሳዕናን  1 ለ 0 በሆነ ውጤት  አሸንፏል። የወላይታ ድቻን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ደጉ ደበበ ከመረብ አገናኝቷል። የጨዋታውን ውጤት ተከትሎ ወላይታ ድቻ በፕሪሚየር ሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ…

በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አንድ ጨዋታ ተካሄዷል። በሜዳው አዳማ ከተማን ያስተናገደው ሲዳማ ቡና ጨዋታውን 3 ለ 2 ማሸነፍ ችሏል። የማሸነፊያ ጎሎችን አማኑኤል እንዳለ፣ ዳዊት ተፈራ እና ሀብታሙ ገዛኸኝ ማስቆጠር ችለዋል።

በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ መቐለ 70 እንደርታን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት የቀኑ ብቸኛ ጨዋታ በመቐለ ተካሄዷል። መቐለ ላይ በተካሄደው ጨዋታ ፋሲል ከነማ መቐለ 70 እንደርታን 2 ለ 0 በማሸነፍ የፕሪሚየር ሊጉ መሪ ሆኗል። የፋሲል ከነማ የማሸነፊያ ግቦች የፕሪሚየር ሊጉን ኮኮብ አግቢነት እየመራ የሚገኘው ሙጅብ ቃሲም በ12ኛ እና 45ኛ ደቂቃዎች ላይ…

ሀዲያ ሆሳዕና አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምን አዲሱ የክለቡ አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሀዲያ ሆሳዕና አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያምን አዲሱ የክለቡ አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ። ከአሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ጋር የተለያየው ሀዲያ ሆሳዕና የቀድሞውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲና አርባምንጭ ከተማ አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያን በምትካቸው ሾሟል። አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነማርያም ዛሬ በክለቡ ጽህፈት ቤት…

ሀዲያ ሆሳዕና የቅጣት ውሳኔ ተላለፈበት

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀዲያ ሆሳዕና የእግር ኳስ ክለብ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈበት። ቅጣቱ ከወልቂጤ ከተማ ጋር በነበረው ጨዋታ አንዳንድ የሀዲያ ሆሳዕና ደጋፊዎች ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጭ ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ ከሜዳ ውጭ ከፀጥታ ሀይሎች ጋር በፈጠሩት ግርግር ምክንያት የተላለፈበት ነው ተብሏል። በተጨማሪም የተወሰኑ ደጋፊዎች የተለያዩ…