Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ቤላሩስ ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሃመድ (ኢ/ር) ከቤላሩስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዚሄንኮቭ ጋር ተወያይተዋል፡፡፡

በውይይታቸውም ሀገራቱ በወታደራዊ እና ጸጥታ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ማስፋትና ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

አይሻ መሃመድ (ኢ/ር) በዚሁ ወቅት÷ ሁለቱ ሀገራት የጋራ እሴት፣ ታሪክና የባህል መመሳሰል ያላቸው መሆኑን አውስተዋል፡፡

ይህንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ የሁለትዮሽ ትብብሩን ይበልጥ ለማሳደግ ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳላት ተናግረዋል፡፡

ማክሲም ሪዚሄንኮቭ በበኩላቸው÷ ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ ስልጠና፣ በመከላከያ ቴክኖሎጂ ልውውጥና በመሳሰሉ መስኮች ያላቸውን ትብብር ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የሀገራቱን ሁለንተናዊ ትብብር  ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውንም የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.