የሀገር ውስጥ ዜና

ከ7 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የኮንትሮባንድ እቃና ዶላር ተያዘ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 1 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ7 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የኮንትሮባንድ እቃና ዶላር መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ዶላሩና እቃው በጉምሩክ ኮሚሽን ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ምሽት ላይ መያዙንም አስታውቋል።