የሀገር ውስጥ ዜና

የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ የኖቤል የሰላም ሽልማት ኢትዮጵያ ስሟና ታሪኳ በዓለም አደባባይ ዳግም ከፍ እንዲል ያደረገ ነው-ጠ/ሚ ጽ/ቤት

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያገኙት የኖቤል የሰላም ሽልማት ኢትዮጵያ ስሟና ታሪኳ በዓለም አደባባይ ዳግም ከፍ ብሎ እንዲታይ ያስቻለ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታወቀ።

የፅህፈትቤቱ የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያገኙቱን 2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት እና በነገው ዕለት የሚደረግላቸውን አቀባበል አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።