ስፓርት

ዋሊያዎቹ በደርሶ መልስ በሱዳን አቻቸው ተሸነፉ

By ዮሐንስ ደርበው

December 25, 2024

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ የመልስ ጨዋታውን በሱዳን 2 ለ 1 ተሸነፈ፡፡

ጨዋታው ዛሬ 11 ሠዓት ላይ በሊቢያ ቤንጋዚ ቤኒና ማርትየርስ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡

ዋሊያዎቹ በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ 2 ለ 0 ዛሬ ደግሞ 2 ለ1 መሸነፋቸውን ተከትሎ በደርሶ መልስ ድምር ውጤት 4 ለ 1 ተረትተው ከውድድሩ ተሰናብተዋል፡፡