ስፓርት

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የበዓል ሰሞን ጨዋታዎች ዛሬም ይቀጥላሉ

By ዮሐንስ ደርበው

December 27, 2024

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የበዓል ሰሞን (ቦክሲንግ ደይ) መርሐ-ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በመርሐ-ግብሩ መሠረት ምሽት 4 ሠዓት ከ30 ላይ ብራይተን ከብሬንትፎርድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

እንዲሁም ምሽት 5 ከ15 አርሰናል ኤሚሬትስ ስታዲዬም ላይ አዲስ አዳጊውን ኢፕስዊች ታውን ይገጥማል፡፡

ትናንት በተደረጉ ጨዋታዎች ሊቨርፑል ሌስተር ሲቲን 3 ለ 1 በማሸነፍ አንድ ቀሪ ጨዋታ እየቀረው መሪነቱን በማጠናከር ከተከታዩ ያለውን የነጥብ ልዩነት በሰባት ማስፋት ችሏል፡፡

እንዲሁም ፉልሃም ቼልሲን 2 ለ1፣ ኖቲንግሃም ፎረስት ቶተንሃም ሆትስፐርን 1 ለ 0፣ ኒውካስል ዩናይትድ አስቶንቪላን 3 ለ 0፣ ዎልቭስ ማንቼስተር ዩናይትድን 2 ለ 0፣ ዌስትሃም ዩናይትድ ሳውዝሃምፕተንን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ከኤቨርተን 1 ለ 1 እንዲሁም ቦርንማውዝ እና ክሪስታል ፓላስ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡