አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ22ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በርካታ ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡
በዚሁ መሠረት ከሦስቱ ጨዋታዎች ቀደም ብሎ በተደረገው መርሐ-ግብር በሜዳው በርንማውዝን ያስተናገደው ኒውካስል ዩናይትድ 4 ለ 1 ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
እንዲሁም በተመሳሳይ ሠዓት በተደረጉት ጨዋታዎች ÷ ዌስትሃም ዩናይትድ በክሪስታል ፓላስ እና ሌስተር ሲቲ በፉልሃም በተመሳሳይ ውጤት 2 ለ 0 ተረትተዋል፡፡
የፕሪሚየር ሊጉን የደረጃ ሠንጠረዥ መሪ ሊቨርፑልን ያስተናገደው ብሬንትፎርድም 2 ለ 0 ተሸንፏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል መሪነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
በሌላ የጨዋታ መርሐ-ግብር ምሽት 2 ሠዓት ከ30 ላይ አርሰናል ከአስቶንቪላ ጋር በኤሚሬትስ ስታዲየም የሚያደርጉት ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡