Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በ800 ሜትር የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ፅጌ ድጉማ ድል ቀናት

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንሳይ ሜዝ በተካሄደ የ800 ሜትር የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ውድድር እትሌት ፅጌ ድጉማ አሸንፋለች፡፡

ፅጌ የ800 ሜትሩን 1 ደቂቃ ከ58 ሴኮንድ ከ97 ማይክሮ ሴኮንድ በመጨረስ በቀዳሚነት ማጠናቀቋን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ ያመላክታል፡፡

ፅጌ ያስመዘገበችው የ800 ሜትር የቦታው ክብረ-ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች ውድድር ደግሞ አትሌት ሳሮን በርሔ 4 ደቂቃ ከ4 ሴኮንድ በመግባት አሸንፋለች፡፡

በተመሳሳይ በወንዶች በተደረገው የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር የታዋቂው የመሰናክል አትሌት ለሜቻ ግርማ ወንድም ኩማ ግርማ የግሉን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል፡፡

ኩማ 3 ሺህ ሜትሩን 7 ደቂቃ ከ31 ሴኮንድ ከ22 ማይክሮ ሴኮንድ በማጠናቀቅ ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል፡፡

 

Exit mobile version