የሀገር ውስጥ ዜና

ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ የሚሳተፉ እንግዶች አቀባበል መርሐ-ግብር ተጀመረ

By Meseret Awoke

February 10, 2025

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለ38ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔና ለ46ኛው የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ የእንግዶች አቀባበል ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

መርሐ ግብሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በተገኙበት በማርች ባንድና በሌሎች የጎዳና ላይ ትርዔትቶች ነው በድምቀት የተጀመረው፡፡

በዛሬው ዕለትም በስራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ ላይ የሚካፈሉ የተለያዩ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችና ሌሎች እንግዶች መግባት ይጀምራሉ።