Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከፋኦ ዳይሬክተር ጄነራል ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት (ዩኤንፋኦ) ዳይሬክተር ጄነራል ኩ ዶንግዩን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ዳይሬክተር ጄነራል ኩ ዶንግዩን በድጋሚ ማግኘታቸውንና በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

በውይይታቸውም፥ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ዘላቂነት እና በዘርፉ ለሚያስፈልገው ጽናት ተባብሮ የመሥራትን አስፈላጊነት በማውሳት የኢትዮጵያን ቀጣይ የግብርና ሥራ ጥረቶችን ተመልክተናል ብለዋል።

Exit mobile version