Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

LONDON, ENGLAND - SEPTEMBER 28: William Saliba of Arsenal and Jamie Vardy of Leicester City compete for the ball during the Premier League match between Arsenal FC and Leicester City FC at Emirates Stadium on September 28, 2024 in London, England. (Photo by Julian Finney/Getty Images)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ዛሬ ሰባት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

በዕለቱ የመጀመሪያ መርሃ ግብር ቀን 9:30 አርሰናል ከሜዳው ውጭ ሌስተር ሲቲን የሚገጥምበት ጨዋታ ይጠበቃል።

በርካታ የፊት መስመር ተጫዋቾቻቸውን በጉዳት ያጡት መድፈኞቹ በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ ለመቆየት የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል።

ማንቸስተር ሲቲ በኢቲሃድ ኒውካስል ዩናይትድን የሚያስተናግድበት ሌላኛው ተጠባቂ ጨዋታ አመሻሽ 12:00 ላይ ይደረጋል።

አስቶን ቪላ ከኢፕስዊች ታውን፣ ፉልሃም ከኖቲንግሃም ፎረስት፣ ሳውዛምፕተን ከቦርንመዝ፣ ዌስትሃም ከብሬንትፎርድ በተመሳሳይ 12:00 የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው።

ክሪስታል ፓላስን ከኤቨርተን የሚያገናኘው የዛሬ የመጨረሻ መርሃ ግብር ምሽት 2:30 ሴልኸረስት ፓርክ ላይ የሚደረግ ይሆናል።

ትናንት ምሽት 5፡00 ላይ ብራይተን ቸልሲን በሜዳው ገጥሞ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል።

Exit mobile version