Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታዳጊዎች ልዑክ የእውቅናና ሽልማት መርሐግብር ተካሄደ

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በመላው ኢትዮጵያ ታዳጊዎች ምዘና ውድድር 2ኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታዳጊዎች ልዑክ የእውቅናና ሽልማት መርሐግብር ተደረገ ።

“የታዳጊ ስፖርተኞች ልማት ለአሸናፊ ሀገር “በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 27 እስከ የካቲት 5 ቀን 2017ዓ.ምበወላይታ – ሶዶ እና አርባ ምንጭ ከተማ በ11 የውድድር ዘርፎች መከናወኑ ይታወቃል፡፡

በውድድሩ በ55 ወርቅ ፣ 50 ብር እና 34 ነሃስ በድምሩ 139 ሚዳሊያዎች በማስመዝገብ 2ኛ ደረጃን ይዞ ላጠናቀቀው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታዳጊ ስፖርተኞች ልዑክ በከተማ አስተዳደሩ የእውቅናና የሽልማት መርሐግብር ተከናውኗል ።

በመርሐግብሩ የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ በላይ ደጀን÷ታዳጊዎች የነገ ሀገር ተረካቢና ተተኪ ስፖርተኞች በመሆናቸው አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በወንድማገኝ ፀጋዬ

Exit mobile version