Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ማንቼስተር ሲቲ ኒውካስል ዩናይትድን በሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ

 

 

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኒውካስል ዩናይትድን አስተናግዶ 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡

 

ለማንቼስተር ሲቲ በጥር የዝውውር መስኮት ክለቡን የተቀላቀለው ግብጻዊው ኦማር ማርሙሽ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሃትሪክ ሲሰራ ማካቴ አራተኛዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡

 

በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች ፉልሃም ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ1፣ ቦርንማውዝ ሳውዝአምፕተንን 3 ለ1፣ ብሬንትፎርድ ዌስትሃም ዩናይትድን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ አስቶንቪላ እና ኢፕስዊች ታውን 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቀዋል፡፡

 

መርሐ ግብሩ ሲቀጥል ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን ይጫወታሉ፡፡

 

Exit mobile version