አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ25ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኒውካስል ዩናይትድን አስተናግዶ 4 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ለማንቼስተር ሲቲ በጥር የዝውውር መስኮት ክለቡን የተቀላቀለው ግብጻዊው ኦማር ማርሙሽ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሃትሪክ ሲሰራ ማካቴ አራተኛዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች ፉልሃም ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ1፣ ቦርንማውዝ ሳውዝአምፕተንን 3 ለ1፣ ብሬንትፎርድ ዌስትሃም ዩናይትድን 1 ለ 0 ሲያሸንፉ አስቶንቪላ እና ኢፕስዊች ታውን 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቀዋል፡፡
መርሐ ግብሩ ሲቀጥል ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን ይጫወታሉ፡፡