የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከፍልሰት ፖሊሲ ልማት ዓለም አቀፍ ማዕከል ሃላፊ ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

February 18, 2025

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከፍልሰት ፖሊሲ ልማት ዓለም አቀፍ ማዕከል ሃላፊ ሞኒካ ዛኔቴ ጋር ተወያዩ።

ውይይቱ፤ በፍልሰት እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት የሚቻልባቸውን አማራጮች መፈለግ ላይ ትኩረት አድርገው መክረዋል።

በተለይም የፍልሰት ፖሊሲ ልማት ዓለም አቀፍ ማዕከል በአዲስ አበባ ቢሮ በሚከፍትበት ሁኔታ ዙሪያ መነጋገራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።