የሀገር ውስጥ ዜና

እስከ አሁን ከ836 ሺህ 253 ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ ተጓጓዘ

By Mikias Ayele

March 24, 2025

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እስከ ትናንት ድረስ 964 ሺህ 118 ነጥብ 1 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ከዚህ ውስጥም 836 ሺህ 253 ነጥብ 2 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን እና 127 ሺህ 864 ነጥብ 9 ሜትሪክ ቶን ደግሞ በወደብ እንደሚገኝ  ሚኒስቴሩ አረጋግጧል፡፡

ወደ ሀገር ውስጥ ከተጓጓዘው መካከልም 523 ሺህ 375 ነጥብ 2 ሜትሪክ ቶን ዳፕ እንዲሁም 312 ሺህ 878 ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የአፈር ማዳበሪያ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡