Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያን የዕዳ ሽግሽግ ጥረት በተመለከተ ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ገለጻ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ እንዲደረግ እያከናወነቻቸው ያሉትን ተግባራት በተመለከተ የገንዘብ ሚኒስቴር ለዋና ዋና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ገለጻ አድርጓል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፥ ተቋማቱ ከኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ ጋር በተጣጣመ ሁኔታ በቀጣይ ለሚከናወኑ ድርድሮች እንዲዘጋጁ አሳስበዋል፡፡

በቅርቡ ከኢትዮጵያ የአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ከስምምነት መደረሱ የተገለጸ ሲሆን፥ የኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ ጥረት በጥሩ ሂደት ላይ መሆኑን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Exit mobile version