Processed with VSCO with a1pro preset

የሀገር ውስጥ ዜና

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለፍቼ ጫምባላላ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

By Hailemaryam Tegegn

March 27, 2025

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለሲዳማ ዘመን መለወጫ – ፍቼ ጫምባላላ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ የሲዳማ ውብ ባህል መገለጫ የሆነው የፍቼ ጫምባላላ በዓል ፍቅር፣ እርቅ፣ ሰላም፣ ምስጋና እንዲሁም ብሩህ ተስፋ የሚሰነቅበት የዘመን መለወጫ በዓል መሆኑን አንስተዋል፡፡

በዓሉ ይበልጥ አንድነቱ የሚጠናከርበት፣ እርቅ፣ ሰላም፣ አብሮነት እና ብሩህ ተስፋ የሚሰነቅበት እንዲሆንም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡