የሀገር ውስጥ ዜና

የአማራ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ በባሕር ዳር ከተማ ከቅዳሜ ጀምሮ ይካሄዳል

By Adimasu Aragawu

March 31, 2025

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአማራ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ከቅዳሜ ጀምሮ እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ የምክክር መድረኩን ከመጋቢት 27/2017 ዓ.ም ጀምሮ በባሕር ዳር ከተማ ለማካሄድ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ባወጣው መረጃ አመላክቷል፡፡