Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሹዋሊድ በዓል ከነገ ጀምሮ በድምቀት ይከበራል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሐረሪ ክልል ከነገ ጀምሮ የሚከበረው የሹዋሊድ በዓል በስኬት ለማጠናቀቅ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ረምዚ ሱልጣን፤ በዓሉ በድምቀት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ከሁሉም ወረዳዎች ከተውጣጡ የጸጥታ አካላት ጋር የጋራ ምክክር በማድረግ ወደ ሥራ መገባቱን አረጋግጠዋል፡፡

በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይኖር ከታች የተዘረዘሩት አካባቢዎች መንገዶች ለትራፊክ ዝግ ይሆናሉ ብለዋል፡፡

በዚሁም መሠረት፡-

በተጨማሪም በዋዜማው ከምሽት ጀምሮ ሥነ-ሥርዓቱ በሚከናወንበት እና ዝግ በሚሆኑ መንገዶች አካባቢ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሠዓት ተሽከርካሪ ማቆም የተከለከለ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version