Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ለናይጄሪያ የመከላከያ ኃይል ከፍተኛ ልዑክ የኢትዮጵያን የልማት ተሞክሮ አጋሩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ለናይጄሪያ የመከላከያ ኃይል ከፍተኛ ልዑክ የኢትዮጵያን የልማት ተሞክሮ አጋሩ።

49 አባላትን ያካተተው የናይጄሪያ መከላከያ ኃይል ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር የሥራ ጉብኝት አድርጓል።

በጉብኝቱ ወቅት ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)፤ በዘላቂ ልማት፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚ መስኮች ኢትዮጵያ የምትሰራቸውን ሥራዎች በተመለከተ ገለጻ በማድረግ ተሞክሮዋን አጋርተዋል።

የልዑካን ቡድኑ አባላት ለተደረገው ገለጻ እና አቀባበል ምስጋና ማቅረባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version