ስፓርት

ኢትዮ ኤሌክትሪክና ሀዋሳ ከተማ አቻ ተለያዩ

By Yonas Getnet

April 09, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሀዋሳ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

የኢትዮ ኤሌክትሪክን ግብ አቤል ሃብታሙ ሲያስቆጥር÷ አሊ ሱሌማን ደግሞ የሀዋሳ ከተማን የአቻነት ግብ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ29 ነጥብ 11ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷ ሀዋሳ ከተማ በ21 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

እንዲሁም 12 ሠዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ስሑል ሽረን በፍቅረየሱስ ተ/ብርሃን ብቸኛ ግብ አሸንፏል፡፡