የሀገር ውስጥ ዜና

የኮሪደር ልማቱ ሠርቶ የመኖር ባህልን እያጠናከረ መሆኑ ተገለጸ

By ዮሐንስ ደርበው

April 09, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኮሪደር ልማት ሥራው የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ሠርቶ የመኖር ባህልን እያጠናከረ መሆኑን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ፡፡

ርዕሰ መሥተዳድሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት፤ “ሠርቶ ጥሮ ግሮ ለሚኖር” ያላቸውን ክብር እና አድናቆት ገልጸዋል፡፡

በክልሉ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራም የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ፤ ሠርቶ የመኖር ባህልን እያጠናከረ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡