የሀገር ውስጥ ዜና

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) የቃሊቲ ሞዴል መናኸሪያ የግንባታ ሂደትን ጎበኙ

By Melaku Gedif

April 11, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒሰትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የቃሊቲ ዘመናዊ ሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ሞዴል መናኸሪያን ጎብኝተዋል፡፡

መናኸሪያው በሰዓት 120 አውቶቡሶችንና 7 ሺህ 200 ተሳፋሪዎችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ተገልጿል።

በውስጡ ካፍቴሪያዎች፣ ሱቆች፣ የስብሰባ አዳራሾች፣ የመመገቢያ ስፍራዎች፣ ከ1ሺህ 130 በላይ የማረፊያ ወንበሮችና የታክሲ ተርሚናል የተዘጋጀለት ማዕከል ነው ተብሏል።

የመናኸሪያው ግንባታ በ3 ነጥብ 9 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፥ በውስጡ ለልዩ ልዩ አገልግሎት የሚውል ባለ አራት ወለል ህንፃ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል።