Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከታንዛኒያ ፕሬዚዳንት የተላከን መልዕክት ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከታንዛኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሐሰን (ዶ/ር) የተላከን መልዕክት ተቀበሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፤ ዛሬ ጠዋት ከፕሬዚደንቷ የተላከውን መልዕክት መቀበላቸውን ገልጸዋል።

መልዕክቱን ያደረሱት የታንዛኒያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና የአሁኗ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሐሰን (ዶ/ር) ልዩ መልዕክተኛ ጃካያ ሚሪሾ ኪክዌቴ (ዶ/ር) መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

Exit mobile version