የሀገር ውስጥ ዜና

የአፍሪካ ቀዳማዊ እመቤቶች ፕሬዚዳንትና ም/ፕሬዚዳንት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

By Mikias Ayele

April 12, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ ቀዳማዊ እመቤቶች ፕሬዚዳንትና የሴራሊዮን ቀዳማዊት እመቤት ፋቲማ ማዳ ባዮ (ዶ/ር) እና የአፍሪካ ቀዳማዊ እመቤቶች ም/ፕሬዚዳንትና የአንጎላ ቀዳማዊት እመቤት ኣና አፎንሳ ዲያስ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸው ወቅት የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግሩም ግርማ አቀባበል ያደረጉላቸው መሆኑን የዓደዋ ድል መታሰቢያ መረጃ ያመላክታል፡፡