Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ማንቼስተር ሲቲ ከመመራት ተነስቶ ክሪስታል ፓላስን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ 32ኛ ሳምንት ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ከመመራት ተነስቶ ክሪስታል ፓላስን 5 ለ 2 አሸንፏል፡፡

በምሳ ሰዓት በተደረገው ጨዋታ ክሬስታል ፓላስ በኤዜ እና ሪቻርድስ ግቦች 2 ለ 0 መምራት ቢችልም ኬቨን ዴብሮይን እና ኦማር ማርሙሽ አከታትለው ባስቆጠሯቸው ግቦች በ2 አቻ ውጤት ወደ እረፍት አምርተዋል፡፡

ከእረፍት መልስ የጨዋታ ብልጫ የነበራቸው ሲትዝኖቹ ኮቫቺች፣ ጆን ማክ አቲ እና ኦሬሊባስቆጠሯቸው ግቦች 5 ለ 2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል፡፡

Exit mobile version