አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ990 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አድርጓል፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንዳሉት÷ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩና በሕግ በተደነገገው አግባብ የይቅርታ መስፈርትን ያሟሉ ናቸው፡፡
ይቅርታ ከተደረገላቸው 990 የሕግ ታራሚዎች መካከል 985ቱ በሙሉ ይቅርታ ከእስር የሚፈቱ ሲሆን÷ ቀሪ 5 ታራሚዎች ደግሞ የእስራት ጊዜያቸው የተቀነሰላቸው መሆኑን ገልፀዋል።
የይቅርታ ተጠቃሚ ከሆኑት የሕግ ታራሚዎች መካከል 73ቱ ሴቶች መሆናቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ÷ 917ቱ ደግሞ ወንዶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ታራሚዎቹ የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል በልማት ሊክሱ እንደሚገባ ማሳሰባቸውንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡