Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሃኖይ እየተገነባ ያለውን የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሃኖይ እየተገነባ የሚገኘውን ትልቅ የዘመነ ከተማ (የስማርት ሲቲ) ፕሮጀክት ጎብኝተዋል።

ይህም ለኢትዮጵያ የከተማ ልማት ሥራ የሚሆን ተሞክሮ የመቅሰም ተግባር አካል መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡

ጉብኝቱ ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ የዘመናዊ ከተማ ፕሮጀክቶችን ለማላቅ የሚደረግ ፍላጎትና ጥረትን ያሳያል ተብሏል።

Exit mobile version