የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግስታት ዘላቂ እድገትን በመደገፍ ረገድ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

By Adimasu Aragawu

April 17, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ከተባበሩት መንግስታት የፕሮጀክት አገልግሎት ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ጆርጅ ሞሪኤራ ዳ ሲልቫ ጋር ተወያይተዋል፡፡

የጽሕፈት ቤቱ ዋና ዳይሬክተሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው÷ ተቋማቸው የኢትዮጵያን የእድገት አጀንዳዎች መደገፍ የሚችልበት አግባብ ላይ ከገንዘብ ሚኒስትሩ ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም የትግራይ ክልልን መልሶ መገንባት ላይ እንዲሁም ዘላቂ እድገትን በመደገፍ ረገድ ሁለቱ ወገኖች በጋራ ለመስራት እና ግንኙነታቸውን ለማጠናከር መስማማታቸውን ጠቁመዋል፡፡