አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ማዕድ አጋርቷል፡፡
ባንኩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ459 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር በላይ ማኅበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት ማዋሉንም አስታውቋል፡፡
የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበበ ከተማ ለሚኖሩ 1 ሺህ ወገኖች በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ፣ የአስኮ እና ፒያሳ የእርዳታ ማዕከላት ማዕድ ማጋራቱን ከባንኩ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡