አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሃኖይ የሚገኘውን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የዓይነስውራን ትምህርት ቤት ጎብኝተዋል፡፡
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ ዛሬ የቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ ቀዳማዊት እመቤት ማዳም ነኹ በሃኖይ የሚገኘውን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የአይነስውራን ት/ቤት አስጎብኝተውኛል ብለዋል፡፡
በጉብኝታቸውም በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ለሚገኘው እና በተለያዩ ክልሎች እየተሰሩ ላሉ አዳዲስ የዓይነስውራን አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚሆኑ ተሞክሮዎች ማግኘታቸውን ገልጸዋል።