Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ቢኬጂ ፋውንዴሽን በተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ማዕድ አጋራ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በላይነህ ክንዴ ግሩፕ ፋውንዴሽን (ቢኬጂ) የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ለወገኖች ማዕድ አጋራ፡፡

በመርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አዲሱ ሻንቆ(ዶ/ር)÷ ቢኬጂ ፋውንዴሽንና ባለቤቱ አቶ በላይነህ ክንዴ የምገባ ማዕከሉን ከመገንባት አንስቶ በየቀኑ 500 ወገኖችን እየመገበ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የምገባ ስራው ተቋርጦ እንደማያውቅ ጠቁመው÷በላይነህ ክንዴ እና ድርጅታቸው ለሚያደርገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የቢኬጂ ፋውንዴሽ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ በላይነህ ክንዴ በበኩላቸው÷ ድርጅቶቻችን ባሉበት ቦታ ሁሉ የአቅማችንን ድጋፍ እያደረግን እንገኛለን ብለዋል።

በተጨማሪም  ትውልድን የሚያንጹ ተቋማትንና መኖሪያ ቤቶችን ገንብተን እያስረከብን እንገኛለን ያሉት አቶ በላይነህ÷ በመስጠታችን በረከትና የህሊና ደስታን እናገኛለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ቢኬጂ ፋውንዴሽን ዛሬ ካከናወነው ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር በተጨማሪ በቡሬ ከተማ ለሚገኙ 1 ሺህ 300 ለሚደርሱ ወገኖች የበዓል መዋያ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ይታወሳል።

በዮሐንስ በቀለ

Exit mobile version