ቢዝነስ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሌጎስ የሚያርገውን ሳምንታዊ በረራ በእጥፍ አሳደገ

By ዮሐንስ ደርበው

April 21, 2025

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ናይጄርያ ሌጎስ ከተማ እያደረገ ያለውን 7 ሳምንታዊ በረራ ከሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ 14 ሳምንታዊ በረራ አሳደገ፡፡

ይህም ለደንበኞቹ ይበልጥ ምቹ የበረራ አማራጭ መስጠት የሚያስችል መሆኑን አየር መንገዱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡