Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአውሶም ላይ የሚመክር ስብሰባ በዩጋንዳ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍና ማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) ዙሪያ የሚመክር ስብሰባ በዩጋንዳ ኢንቴቤ መካሄድ ጀምሯል።

በስብሰባው ለአውሶም ሰራዊት ያዋጡ ሀገራት ተወካይ ልዑኮች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ኢትዮጵያ በመወከል በመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) የተመራ ልዑክ እየተሳተፈ እንደሚገኝ ከኡጋንዳ ኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version