ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በኖቤል የሰላም ማዕከል በተዘጋጀው “ክሮስ ሮድስ ኢትዮጵያ የፎቶ ዐውደ ርዕይ ጎበኙ
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 1 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኖቤል የሰላም ማዕከል በተዘጋጀው “ክሮስ ሮድስ ኢትዮጵያ” (ኢትዮጵያ በመስቀለኛ መንገድ) ላይ የተሰኘውን የፎቶ ዐውደ ርዕይ ጎበኙ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር የተገኙበት የፎቶ አውደርዕይ መክፈቻ ስነስ ስርዓት ነበር፡፡