Fana: At a Speed of Life!

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል ተጀመረ

 

 

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሰባት አመታት ተቋርጦ የነበረው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀምሯል።

 

በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ(ፕ/ር) ÷የስፖርት ፌስቲቫሉ መዘጋጀቱ ጥቅሙ የጎላ መሆኑን አንስተዋል፡፡

 

በአምስት የስፖርት አይነት ከ 49 የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ ተማሪዎች የሚሳተፉበት ይህ ውድድር ተማሪዎችን እርስ በርስ የሚያስተሳስር እና የሚያቀራርብ እንደሆነ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ መክዩ መሃመድ ተናግረዋል።

 

ደማቅ በነበረው የመክፈቻ ስነ -ስርዓት ተማሪዎችም የመጡበት አካባቢ የሚወክል ባህላዊ ትርዒት አሳይተዋል።

 

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የሚካሄደው ይህ ውድድር ጥር 27 ቀን 2017ዓ.ም ፍፃሜውን ያገኛል።

 

በዳዊት መሃሪ

 

 

 

 

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.