ሌስተር ሲቲ ቶተንሃምን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር 11 ሰዓት ላይ ቶተንሃምን ከሌስተር ያገናኘው ጨዋታ በሌስተር ሲቲ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
ቶተንሃም በሊጉ ካደረጋቸው 23 ጨዋታዎች 7 ብቻ ያሸነፈ ሲሆን በ13 ጨዋታዎች ተሸንፎ በ24 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ክሪስታል ፓላስ በሜዳው ከብሬንትፎርድ ጋር ተጫውቶ 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡