ማንቼስተር ዩናይትድ ፓትሪክ ዶርጉን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ወጣቱን ተከላካይ ፓትሪክ ዶርጉን ከጣሊያኑ ክለብ ሊቼ በ35 ሚሊየን ዩሮ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
የ20 ዓመቱ ዴንማርካዊ ተከላካይ በዩናይትድ እስከ ፈረንጆቹ 2030 የሚያቆየውን ውል ፈርሟል።
በሌላ የዝውውር መረጃ የማንቼስተር ዩናይትዱ ተጫዋች ማርከስ ራሽፎርድ አስቶን ቪላን በውሰት ለመቀላቀል መስማማቱ ተገልጿል።
በኃይለ ማርያም ተገኝ