የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ላለፉት 10 ቀናት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው የተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡
በተጨማሪም በምስጉን ዋንጫ የአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተሸላሚ ሆኗል።
በማጠቃለያ መርሐግብሩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ (ዶ/ር)÷ የውድድሩ ጠቀሜታ የጎላ በመሆኑ ሊቋረጥ እንደማይገባ ተናግረዋል፡፡
ለውድድሩ መሳካት የበኩላቸውን ድርሻ ለተወጡ አካላትም ሚኒስቴር ዴኤታው ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በአምስት የተለያዩ የውድድር አይነቶች በ49 ዩኒቨርሲቲ መካከል በተካሄደው ውድድር 2 ሺህ 500 ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነውበታል ።
በዳዊት መሐሪ