በ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቼክ ሪፐብሊክ ኦስታርቫ ከተማ በተካሄደው የዓለም የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ አሸንፋለች፡፡
አትሌት ፍሬወይኒ የርቀቱን በ8 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ ከ17 ማይክሮ ሰከንድ በመጨረስ ነው ማሸነፍ የቻለችው፡፡
የ1 ሺህ 500 ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር የክብረ ወሰን ባለቤቷ ፍሬዌኒ ኃይሉ በኦስታርቫ ያስመዘገበችው ውጤት የቦታው ፈጣን ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡