Fana: At a Speed of Life!

ሚኒስቴሩ ለ7 ሚሊየን ዜጎች የሚያገለግሉ የውሃ ጥራት መመርመሪያ ኪቶችን በድጋፍ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥር 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት ለኢትዮጵያ የውሃ ጥራት መመርመሪያ ኪቶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በርክክቡ ወቅት እንዳሉት÷ የውሃ ጥራት መመርመሪያ መሳሪያዎቹ የውሃ ብክለትን ቀድመው በመለየት ኮሌራን ጨምሮ የውሃ ወለድ በሽታዎችን ለመቀነስ ያስችላሉ፡፡

ኪቶቹ 23 የኮሌራና ሌሎች የአደጋ ጊዜ ተጠቂ ወረዳዎችን በመለየት እንደሚሰራጩ ጠቁመው÷በሁሉም ክልሎች በአማካይ እስከ 7 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠት ያስችላሉ ብለዋል።

የፍተሻ ኪቶች የክልል ጤና ቢሮዎችና የወረዳ ጤና ጽ/ቤቶችን የውሃ ጥራት ክትትል አቅም ለማሳደግ ሚናቸው ጉልህ ነው መባሉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.