Fana: At a Speed of Life!

ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ከናይጄሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ከሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር)  ከናይጀሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሱፍ ማይታማ ተገር ጋር  በሁለትዮሽ እና አሕጉራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

 

ሚኒስትሮቹ  በውይይታቸው የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልባቸው መስኮች ላይ መክረዋል።

 

በተመሳሳይ  ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ከሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ሞሀመድ ኦማር ጋር  ባደረጉት ውይይት በሁለትዮሽ እና በአካባቢያዊ የሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.