Fana: At a Speed of Life!

ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኬንያ እና ዚምባብዌ አቻቸው ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ46ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ የአስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ጎን ለጎን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከኬንያ እና ዚምባብዌ አቻቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስትሩ ከኬንያ የውጭ እና የዳያስፖራ ጉዳዮች ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ(ዶ/ር) ጋር ባደረጉት ውይይት በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡
በተጨማሪም ሚኒስትሩ ከዚምባቡዌ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሞን ማሪዋራ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይታቸውም ሳይካሔድ ቆይቶ የነበረውን የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን መልሶ በማንቀሳቀስ እና አዳዲስ የትብብር መስኮችን አካቶ መሥራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.