የዚምባቡዌ ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የአፍሪካ ህብረት የመሪዎቸ ጉባዔ ከፊታችን የካቲት 8 እስከ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድ ይታወቃል።
በመሰረት አወቀ እና ብሩክታዊት አፈሩ