Fana: At a Speed of Life!

የ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ተገልጋይ ፋይሎች በአዲስ መልክ ተደራጅተው አገልግሎት እየተሰጠ ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመረጃ አያያዝ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆንና የሚፈለጉ መረጃዎች በቀላሉ እንዲገኙ ለማድረግ የ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ተገልጋይ ፋይሎች በቴክኖሎጂ በመታገዝ በአዲስ መልክ ተደራጅተው አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ የአስተዳደሩን የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም እያቀረቡ ያሉት ከንቲባዋ÷ ከተማዋ ለነዋሪዎቿ ከምትሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ ዓለም አቀፍ፣ አህጉር አቀፍና ሀገር አቀፍ ሚናዋን የሚመጥን፣ የከተሜነት ይዘት እንዲኖራት በርካታ ጥረቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል፡፡

በ6 ወራት እቅድ አፈጻጸም መሰረት በከተማዋ የሚታዩትን ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስና ዘመን ያስቆጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት በማድረግ ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏልም ነው ያሉት፡፡

የመረጃ አያያዝ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆንና የሚፈለጉ መረጃዎች በቀላሉ እንዲገኙ የሚያደርግ የ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ተገልጋይ ፋይሎች በቴክኖሎጂ በመታገዝ በአዲስ መልክ ተደራጅተው አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በየሻምበል ምህረት

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.