በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል በዌስትሃም ተሸነፈ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሜዳው ዌስትሃም ዩናይትድን ያስተናገደው አርሰናል 1 ለ ዐ ተሸንፏል።
የዌስትሃምን የማሸነፊያ ጎል ጃሮድ ቦውን በ45ኛ ደቂቃ ሲያስቆጥር፥ ከአርሰናል በኩል ወጣቱ ተከላካይ ሊውስ ስኬሊ በሁለተኛው አጋማሽ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
በሌሎች የ12 ሰዓት ጨዋታዎች፣ ብራይተን ሳውዛምፕተንን 4 ለ ዐ፣ቶተንሃም ሆትስፐር ኢፕስዊች ታዎንን 4 ለ1፣ ክርስታል ፓላስ ፉልሃምን 2 ለ 0 እንዲሁም ዎልቭስ ቦርንማውዝን 1 ለ ዐ አሸንፈዋል።
በሌላ በኩል ከደቂቃዎች በኋላ 2:30 ቼልሲ ከሜዳው ውጪ አስቶን ቪላን የሚገጥምበት ጨዋታ ይጠበቃል።