Fana: At a Speed of Life!

ፈተናዎችን በመሻገር ጠንካራ ሀገር ለመገንባት የዓድዋ ድልን መጠቀም አለብን – አይሻ መሀመድ (ኢ/ር)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ያጋጠሙንን ፈተናዎች በመሻገር ጠንካራና የበለጸገች ሀገር ለመገንባት የዓድዋ ድልን መጠቀም እንደሚገባ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) ገለጹ፡፡

129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል” በሚል መሪ ቃል በዓድዋ መታሰቢያ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል።

የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) በበዓሉ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት÷ አንድነታችንን በማጠናከርና የገጠሙንን ፈተናዎች በመሻገር ጠንካራና የበለፀገች ኢትዮጵያና አፍሪካን ለመገንባት መጠቀም ይገባል ብለዋል።

ዓድዋ የምንዘክረው ታሪክ ብቻ ሳይሆን ለትውልድ የምናወርሰው ታላቅ ሃላፊነት ነው ያሉት ሚኒስትሯ÷ ዓድዋ አፍሪካዊያን ለነፃነት የሚያደርጉትን ንቅናቄ በማቀጣጠል ለድል እንዳበቃቸው ገልጸዋል፡፡

ዛሬም በህብረትና በጀግንነት በመነሳሳት ለሀገራችንና ለአፍሪካ ብልፅግና ለማረጋገጥ መትጋት እንደሚገባ ማሳሰባቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.