Fana: At a Speed of Life!

የእንግሊዝ ኩባንያዎች በኢኮኖሚ ማሻሻያው የተፈጠረውን ምቹ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ የተፈጠረውን ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድል እንዲጠቀሙበት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ፡፡

በእንግሊዝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስተባባሪነት የተዘጋጀው የኢትዮጵያና እንግሊዝ የቢዝነስ ፎረም በለንደን ተካሂዷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምሥጋኑ አርጋ በዚሁ ወቅት፥ በኢትዮጵያ የተከናወኑ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች የፈጠሩትን ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድል የእንግሊዝ ኩባንያዎች እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል።

በፎረሙ ላይ በርካታ የእንግሊዝ ኩባንያዎች የተሳተፉ ሲሆን፥ በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችና የመንግሥት ፖሊሲዎች ዙሪያ ገለጻ መደረጉን ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.